!
ልቅ ምዕራፍ : - ክፍል አንድ
ከሥርጉተ
ሥላሴ
በመከራው
ሁሉ ተደስቶ የኖረው
የብፁእ የቅዱስ
ጳውሎስ መልዕክት ወደ
ሮሜ ሰዎች
ደግሞ
አቀበት ፣ መቃተት፣
በምጥ መዋጥ :: የጥያቄ
ምልክት:: ሠርዶ መሳይ
ሰንበሌጥ ልምሰል ያለ
የውሸት ቅብ:: ለበጣ::
የእበት ልቅልቅ ዓይነት
በቃ እንደነገሩ:: ሲጥ ሲጥ :: ሲጥጥ -
ሲጥጥ :: አርባውን
አስቀድሞ ያወጣ፣
በቁሙ ተስካር ያበላ::
በሞትና በሕይወት
መካከል ያለ ደመ
ነፍሱን የተገተረ
የዛሬ 300 ዓመት
ሊያልፍም የሚችል የአሽዋ
ድርድር :: ገና ከሩቅ
ሲያዩት ያኮረፈ ቃሬዛ
ላይ ያለ፣ ለኑዛዜ
የተሰናዳ ህንጣ ::
አስታማሚ ሳይፈልግ
ታማሚ፣ መድኀኒት
የማይሻው በሽተኛ ህንጣ፣
ከፊት ለፊቱ ካለው
አንድ የምግብ የዕቃ
መደበር ሜግሮ ላይ
ሆኜ ተመለከትኩት
እንደ ከፋው
ነው:: በስተጀርባው
ሆኜም ከ605 አውቶብስ
መናኸሪያ ቆም ብዬም
አየሁት::በደረቱ ላይ
ሁሌ በሚፈሱት
እንባዎቹ ጠቁሯል::
አረንጓዴ ገላዎቹን
ክፉኛ አበልዞታል:: በዚህም
ክፉኛ አዝነዋል::
አስተዛዛኝም ሆነ ምሾ
ደርዳሪ ግን አላሰኘውም::
እንደገናም
በሁለቱ ጎኖቹ ያሉትን
የመተንፈሻ
ቧንቧዎቹንም ጥቂት
ጠጋ ብዬ
ተመለከትኳቸው::
ተፈርዶባቸዋል:: ውሀ
ሲሄድባቸው የከረሙ
ዓለቶች መስለዋል::
ለዘር ለብጣሽ ለዛ
የሚባል ነገር
አልፈጠረለትም::
ታሬና ቁንጮው
ሻግቷል:: ሸጋታው ራሱ መከራን
ይጠራል እንጂ ደስታን
አይፈጥርም::የሀዘን
ሲቃን ያቃብጣል እንጂ
ተስፋን ፈጽሞ
አይቸርም::የደረቀ
ተስፋ
መናኸርያ::እኔም
እንደ እሱ ደመ ነፍስ
ሆኜ አለሁ:: በሱ
ልከዘን
ተፈርዶብኛልና :: ወደ
ውስጥ ዘለቅሁ::
እግሮቼ የእኔ
አልመሰሉኝም::
ከብደውኛል::
አዘቅዝቄ
ተመለከትኳቸው:: እረ
በዕይታ ቀመራዊ ሂደት
እኔ ላለሁበት
ያትውልድ ፈንገጥ ብዬ
እንደምኖር እሱ እራሱ
ለክፍት ጫማ
የተፈጠሩት ውብ
ተረከዞቼ ከነ
መሀባቸው መሆናቸውን
አረጋገጥኩ::
... ግን ወደ
አይቀሬው አፍ ወዳለው
መቃብር ቤት ገሠገስኩ
ክብድ አለኝ:: ፍራው/
ወይዘሮ ሹቱደር
ማርጋሪን የስደተኛው
ካምፕ ኃላፊ ክፍሌን
ከፈቱልኝ:: በእውነት
አያስገባም እምል -
የእምል ድልብ
ተሽቀዳድሜ ብለቅ ጥሩ
አድርጎ
ያስታመማቸውን ሁለት
ባለ እንጨት መስኮቶች
ከፈትኳቸው:: እንደ ነገሩ
ናቸው:: ፈቃድ ተሰጠኝ ወይም
መቆም ወይ መቀመጥ::
የቁም እስር አይነት
መላወሻ የላትም
ክፍሏ:: ጣሪያ
ግድግዳውን ተመለከትኩት::
ውር ውር የሚሉ
ጉዶች አሉበት:: ገለጥ
አድርጌ አየኋቸው::
እንዴት ነሽ ለማለት
ይሆን ? ደነሱብኝ:: በተገነጠለው
የግድግዳ ካርቶን
ውስጥ ገለጥ አድርጌ
ተመለከትኩት:: በመቶ
የሚቆጠሩ የበረሮ
ክምችቶች የሠርግና
የምላሽ ቀናቸው
ነበር:: ባለ ቬሎ ... ባለ
ክሬም ...
ኃይለኛ
ወጀብ አዘል ዝናብ
ያን በምርኩዝ
ተንገዳግዶ የቆመውን
መስኮት ገፍትሮ በጥፊ
አጮለኝ:: እንጨቶቹ ድንኳን
ተጥሎላቸዋል::
ሳልስት ላይ
ተቀምጠዋል:: ወይ
አንተ ወይ እኛ ግን መቼ
ይባባላሉ:: ከዚያ
ጉደኛ ወጀብ ጋር
የጥያቄ ምልክት
በመስመርና በስንጥቅ፣
በስንጥርና በፍንጭት
ሽርሽሩ ቀለጠ::
በመላጣ ተስፋ ወጣ
ገባ፣ ገባ ወጣ ጨዋታ::
ሻታ ይዞራል ታካች
የጥያቄ ምልከት::
ከባህር ወላል ታችና
ላይ፤ ላይና ታች
የጠቆረ ጥቃቅን
ድሪቶአማ ቅዝቃዜ
ሩሄን ፋታ ነሳት::
መከራ
የገረፈው መስታወትም
ፊት ለፊቴ ተገትሯል::
ጠንጋራ! ነገ ሌላ ቀን
ነው በማለት ቀጣዩን
ዘመን ካሳለፍኩት
ጨጎጎታማ ዘመን ጋር
እንዳመሳክርለት
አቤቱታውን አቀረበ::
ሱባኤው ከአንተ ጋር
ብገባ ይሻል ይሆን
የጥያቄ ምልክት!
ድህና በሚባልለት
ጥቂት አካሉ ላይ
ተግትሬ ራሴን
አየሁት::
በኢማጅኔሽን
የማልኖር፣ የራሴ
ምንገድ ያለኝ ራሴን
መርምሬ የተገነዘብኩ
ፍላጎቴን የማውቅ
እውነት ፈላጊ ቋሚ
ባህርይ ያለኝ፣
በአርቲፊሻል
የትናንት የዛሬ ምን
አልባትም አርጅቶ
በሚመጣው የነገ
ገጠመኝ ራሴን ሸንግዬ
መኖር የማልችል በ
አስተሳሰብ፣ በጉዞ በሀዘን እና
በምሬት የማረተው
መስታወቴ አሳምሮ
ነገረኝ:: አዎ
በጭላጭል የነበረችው
ትንሽ ብጣቂ ሻማ
አንቀላፋች ግን ለምን
የጥያቄ ምልክት::
ይቀጥላል . . .